የኢትዮጵያ ፖስታ የ2017 በጀት አመት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2018 በጀት አመት እቅድ ውይይት አካሄደ።

ለሁለት ቀናት በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም በድርጅቱ የስትራቴጂክ ምሰሶዎች ላይ ተመስርቶ የቀረበ ሪፖርት እና የቀጣይ በጀት አመት እቅዶች በስፋት የተቃኙበት ነበር። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ2017 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም የተመዘገበበት እንደሆነ የተነሳ ሲሆን እንደተቋም በቀጣይ ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል ተብለው በዝርዝር የቀረቡ ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል፡፡

በቀርቡት ሪፖርቶች መሰረት ሊስተካከሉ እና ሊጠናከሩ ይገባቸዋል የተባሉ የስራ ማዕቀፎች ላይ ያተኮሩ ገለጻዎች የተካተቱ ሲሆን እርምት ይፈልጋሉ በተባሉ ነጥቦች ላይም ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በቀጣይም የ2018 በጀት ዓመት ሊሰሩባቸው በታሰቡ እቅዶች ላይ ጥልቅ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በመድረኩ ላይ በ2017 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶች የዋንጫ፣ የሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በውይይቱ መጠናቀቂያ ላይም የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እንደ ተቋም ለተቀመጠው የ2018 በጀት ዓመት እቅድ በአዲስ ጉልበት እና መነሳሳት ራዕያችንን በትጋት ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ ከታለመለት ከፍታ ላይ ለማድረስ ከሁሉም የድርጅቱ ሰራተኞች ትጋት እና አገልጋይነት የሚጠበቅ መሆኑን ገልፀዋል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Read More »