የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተደረሰው ስምምነት እንደተቋም በኢትዮጵያ ፖስታ የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ ፕላን ላይ ትልቅ እመርታን የሚያመጣ መሆኑን ገልፀው በቅርቡ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። በዝግጂቱ ላይ የኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ይለበስ አዲስም በበኩላቸው ተቋማቸው ከኢትዮጵያ ፖስታ ጋር ይሕን ስምምነት በማድረጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው የኦን ላይን ግብይት አከፋፈል ስርአቱን እና የውክልና ባንኪንግ ስራን (agency banking ) በእጅጉ ሊያግዝ የሚችል እንደሚሆን ገልፀዋል።

በተያያዘም ይህን ስምምነት ከታለመለት ግብ ለማድረስ የማስፈጸሚያ ሰነድ ( functional specification document ) በኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮመርሺያል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና በኢትስዊች ቺፍ ፖርቲፎሊኦ ኦፊሰር አቶ አቤኔዘር ላቀው በኩል ተፈርሟል። መጨረሻም በሁለቱም ተቋማት በኩል ለዚህ ስምምነት መሳካት ጥረት ያደረጉ አካላት ምስጋና ተችሯቸዋል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »