የሩሲያው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት አደረገ።

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስተባባሪነት መቀመጫውን ሩሲያ ላይ ያደረገው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ተገኝተው ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

የ RWB ልኡካን ቡድን የኢትዮጵያ ፖስታ ሲደርስ በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በከፍተኛ አመራር ቡድኑ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

በውይይቱ ላይም አለም ዓቀፍ የኢ-ኮሜርስ ንግዱ ላይ ሁለቱ አጋር ድርጅቶች በጋራ ሊሰሩባቸው ስለሚችሉ ነጥቦች በማንሳት ጥልቅ ውይይት አድርገዋል፡፡

ከውይይቱም ባሻገር የልኡካን ቡድኑ አባላት በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራአስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በከፍተኛ አመራር ቡድኑ አማካኝነት የተለያዩ የኢትዮጵያ ፖስታን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች የሥራ ሁኔታ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ መጋዘኖችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱም ወቅት ጎብኚዎቹ በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ የተመለከቱት የአሠራረር ሁኔታ ከጠበቁት በላይ እንደሆነ እና ደስ እንደተሰኙበት ተናግረው በቀጣይ በጋራ ሊሠሩባቸው የሚችሉባቸውን መንገዶች ማመቻቸት እና ወደሥራው መግባት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »