የሩሲያው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት አደረገ።

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስተባባሪነት መቀመጫውን ሩሲያ ላይ ያደረገው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ተገኝተው ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

የ RWB ልኡካን ቡድን የኢትዮጵያ ፖስታ ሲደርስ በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በከፍተኛ አመራር ቡድኑ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

በውይይቱ ላይም አለም ዓቀፍ የኢ-ኮሜርስ ንግዱ ላይ ሁለቱ አጋር ድርጅቶች በጋራ ሊሰሩባቸው ስለሚችሉ ነጥቦች በማንሳት ጥልቅ ውይይት አድርገዋል፡፡

ከውይይቱም ባሻገር የልኡካን ቡድኑ አባላት በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራአስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በከፍተኛ አመራር ቡድኑ አማካኝነት የተለያዩ የኢትዮጵያ ፖስታን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች የሥራ ሁኔታ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ መጋዘኖችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱም ወቅት ጎብኚዎቹ በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ የተመለከቱት የአሠራረር ሁኔታ ከጠበቁት በላይ እንደሆነ እና ደስ እንደተሰኙበት ተናግረው በቀጣይ በጋራ ሊሠሩባቸው የሚችሉባቸውን መንገዶች ማመቻቸት እና ወደሥራው መግባት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »