የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የመታሰቢያ ቴምብሮቹንም የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በጋራ በመሆን ይፋ አድርገዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አንጋፋው የኢትዮጵያ ፖስታ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ታሪኮች በተለያዩ ጊዜያት በቴምብር ሥራዎች እየቀረጸ ሲያስቀምጥ የኖረ ተቋም እንደሆነ ገልጸው ዩኒቨርሲቲያቸውም ከኢትዮጵያ ፖስታ ጋር በመስራቱ ኩራት እና ደስታ እንደሚሰማው ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም የተቋማትን የዘመናት አበርክቶት ለአለም በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ያለው እና የሚገኘው የኢትዮጵያ ፖስታ ሌሎች ዝግጅታቸው የተጠናቀቁ የተቋማት ቴምብሮችን ከተቋማቱ ጋር በመሆን በየጊዜው ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚያደርግ እና አሁንም ይህንኑ አገልግሎት ለሚሹ ተቋማት በሩ ክፍት እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »