የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የመታሰቢያ ቴምብሮቹንም የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በጋራ በመሆን ይፋ አድርገዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አንጋፋው የኢትዮጵያ ፖስታ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ታሪኮች በተለያዩ ጊዜያት በቴምብር ሥራዎች እየቀረጸ ሲያስቀምጥ የኖረ ተቋም እንደሆነ ገልጸው ዩኒቨርሲቲያቸውም ከኢትዮጵያ ፖስታ ጋር በመስራቱ ኩራት እና ደስታ እንደሚሰማው ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም የተቋማትን የዘመናት አበርክቶት ለአለም በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ያለው እና የሚገኘው የኢትዮጵያ ፖስታ ሌሎች ዝግጅታቸው የተጠናቀቁ የተቋማት ቴምብሮችን ከተቋማቱ ጋር በመሆን በየጊዜው ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚያደርግ እና አሁንም ይህንኑ አገልግሎት ለሚሹ ተቋማት በሩ ክፍት እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »