የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኦሮሚያ ጤና ቢሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ።

የኢትዮጵያ ፖስታ  ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመገናኘት በክልሉ የሚገኙ የጤና ናሙና ሎጂስቲክስ፣ የፋይናንሺያል እና የመልዕክት አገልግሎቶችን በቅንጅት መስጠት ላይ ያተኮረ የትብብር ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሂዷል። የኢትዮጵያ ፖስታ ላለፉት አስር አመታት ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በመላ ሀገሪቱ ከሚገኙ የመንግስት የጤና ተቋማት የጤና ናሙናዎችን ተቀብሎ ወደ መመርመሪያ ጣቢያዎች በማድረስና ውጤቱንም መልሶ ለጤና ተቋማት በማስረከብ የሎጅስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ይህ አሰራር በናሙና ዝውውር ላይ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ለህብረተሰቡ የጤና ሽፋንን ከመጨመር አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል።

በኦሮሚያ ጤና ቢሮ ስር ከሚገኙ የዞንና ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊዎች ጋር  የተደረገው ይህ ውይይት የጤና ናሙና ሎጂስቲክስን በቴክኖሎጂ ማዘመንና አጋርነትን ከፍ በማድረግ ለህብረተሰቡ ይበልጥ ተደራሽ መሆን ላይ ያተኮረ ነበር። ይህንንም ለመተግበር የኢትዮጵያ ፖስታ በኦሮሚያ ጤና ቢሮ ሥር በሚገኙ 1440 የጤና ተቋማት ውስጥ የአገልግሎት መስጫ ቦታዎችን ለማግኘት የሚያስችል ስምምነት ላይ ተደርሷል። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ  የኢትዮጵያ ፖስታ የናሙና አሰባሰብ ሂደቱን ለማቀላጠፍ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጨማሪ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በነዚህ የጤና ተቋማት ውስጥ አገልግሎት መስጫ ጽ/ቤቶችን በማቋቋም አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »