የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝት፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንጦጦ በሚገኘው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና የምርምር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በማዕከሉ ጉብኝታቸው ወቅት ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና ወደፊት የሳተላይት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሊሰሩ በታቀዱት ስራዎች ላይ ትልቅ እምነት እና ተስፋ እንዳሳደሩም ገልፀዋል።

በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም እንዲሁ በማዕከሉ ጉብኝታቸው መደሰታቸውን ገልጸው ለነገዋ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ መሠረትነት ጉልህ ሚና የሚጫወት ተቋም በመጎብኘታቸው እና በሥራ አጋርነት አብረው መስራት በመቻላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሀይ ለተጋባዥ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በጉብኝቱም ወቅት በማዕከሉ ስለሚከናወኑ የምርምር ተግባራትና የሳተላይት መረጃዎችን በመሰብሰብ ለተለያዩ አካላት መረጃዎችን በመስጠት እያበረከተ ስላለው አስተዋፆኦ በዝርዝር ገለጻ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ የሚታወስ ነው።

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »