የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝት፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንጦጦ በሚገኘው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና የምርምር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በማዕከሉ ጉብኝታቸው ወቅት ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና ወደፊት የሳተላይት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሊሰሩ በታቀዱት ስራዎች ላይ ትልቅ እምነት እና ተስፋ እንዳሳደሩም ገልፀዋል።

በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም እንዲሁ በማዕከሉ ጉብኝታቸው መደሰታቸውን ገልጸው ለነገዋ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ መሠረትነት ጉልህ ሚና የሚጫወት ተቋም በመጎብኘታቸው እና በሥራ አጋርነት አብረው መስራት በመቻላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሀይ ለተጋባዥ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በጉብኝቱም ወቅት በማዕከሉ ስለሚከናወኑ የምርምር ተግባራትና የሳተላይት መረጃዎችን በመሰብሰብ ለተለያዩ አካላት መረጃዎችን በመስጠት እያበረከተ ስላለው አስተዋፆኦ በዝርዝር ገለጻ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ የሚታወስ ነው።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »