በኢትዮጵያ ፖስታ እና በቲና ማርት መካከል የጋራ መግባቢያ ሠነድ ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በኦን ላይን የግብይት ስርዓቱ ላይ በአጭር ግዜ ውስጥ ትልቅ ልዩነትን እየፈጠረ ከሚገኘው ቲና ማርት ጋር አብሮ የመስራት ስምምነት ተፈራርሟል።

በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና የ ቲና ማርት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን መካከል የተፈረመው ስምምነት አላማ ደንበኞች በቲና ማርት ድረ-ገፅ እንዲሁም ሞባይል መተግበሪያ ገብተው ለሚያዟቸው የመዋቢያ እቃዎች፣ልብሶች እንዲሁም የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁሶች በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ያሉበት ድረስ ማድረስ ማስቻል መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት በቀለ የኢትዮጵያ ፖስታ ከጀመረው የዲጂታል ገበያ ትግበራ እንዲሁም ካለው የአመታት የሎጅስቲክስ ልምድ አንፃር ይህ ስምምነት ለደንበኞች የሚቀርቡ አገልግሎቶችን በዘመናዊ ሁኔታ ለማሳለጥ የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል።

የቲና ማርት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን በበኩላቸው ከ131ዓመታት በላይ ልምድ ባለው በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ትእዛዞች የማድረስ ስራውን በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱ ለድርጅታቸው ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን እና ለደንበኞችም ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው እንደሆነ ገልፀዋል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »