በኢትዮጵያ ፖስታ እና በቲና ማርት መካከል የጋራ መግባቢያ ሠነድ ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በኦን ላይን የግብይት ስርዓቱ ላይ በአጭር ግዜ ውስጥ ትልቅ ልዩነትን እየፈጠረ ከሚገኘው ቲና ማርት ጋር አብሮ የመስራት ስምምነት ተፈራርሟል።

በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና የ ቲና ማርት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን መካከል የተፈረመው ስምምነት አላማ ደንበኞች በቲና ማርት ድረ-ገፅ እንዲሁም ሞባይል መተግበሪያ ገብተው ለሚያዟቸው የመዋቢያ እቃዎች፣ልብሶች እንዲሁም የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁሶች በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ያሉበት ድረስ ማድረስ ማስቻል መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት በቀለ የኢትዮጵያ ፖስታ ከጀመረው የዲጂታል ገበያ ትግበራ እንዲሁም ካለው የአመታት የሎጅስቲክስ ልምድ አንፃር ይህ ስምምነት ለደንበኞች የሚቀርቡ አገልግሎቶችን በዘመናዊ ሁኔታ ለማሳለጥ የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል።

የቲና ማርት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን በበኩላቸው ከ131ዓመታት በላይ ልምድ ባለው በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ትእዛዞች የማድረስ ስራውን በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱ ለድርጅታቸው ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን እና ለደንበኞችም ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው እንደሆነ ገልፀዋል።

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »