የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

በ 1967 ዓ.ም የተቋቋመው ታሪካዊው የፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመቱን በዛሬው እለት በድምቀት አክብሮ ውሏል፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች እና ታላላቅ የሃገራችን ሰአሊያን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም በፖስታ ሙዚየሙ ላይ ሊሠሩ ከታቀዱት የማስፋፊያ ሥራዎች አኳያ የባለድርሻ አካላቱ ሃሳብ እና እገዛ እንደሚያስፈልግ እና በብዙ መልኩ ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ መሆኑንም ጠቅሰው ለታዳሚው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የፖስታ ሙዚየሙ ሱፐርቫይዘር የሆኑት አቶ ደረጀ ብርሃኑ ለተሳታፊዎቹ በሙዚየሙ ውስጥ ያሉትን 50 ዓመታትን ያስቆጠሩ የቴምብር ሥራዎችን አስጎብኝተው በቅርቡ በካታሎግ መልክ ተዘጋጅተው ለጎብኚዎች እንዲደርሱ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዚሁ ክብረ በዓል ላይ የተገኙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ማለትም አቶ አሰፋ ጉያ፣ የሰዓሊ ቦጋለ በላቸው ቤተሰቦች እንዲሁም ሌሎች አንጋፍ አርቲስቶች በመድረኩ ላይ የፖስታ ሙዚየሙ አሁን ላለበት ደረጃ መድረስ በየደረጃው ያሉ የኢትዮጵያ ፖስታ የስራ መሪዎችን አመስግነው ሙዚየሙን ለማዘመን እና ለማስፋፋት በሚደረገው ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ከኢትዮጵያ ፖስታ ጎን በመቆም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል፡፡

በመጨረሻም የፖስታ ሙዚየሙ የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል በቀጣይም ለአንድ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ እንደሚቀጥል እና ጎብኚዎችም መጥተው እየጎበኙ የዚህ ታሪክ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል፡፡

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »