የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

በዚሁ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮመርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በቀለ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍን ዲጂታላይዝና ዘመናዊ ከማድረግ አኴያ ኢትዮጵያ ፖስታ እየተጫወተ ስላለው ጉልህ ሚና አስረድተዋል። በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ በአለም አቀፍ የንግድ ማእከል እና #ICTET የተዘጋጀው ወርክሾፕ ፣ የ #AfCFTA (የአፍሪካ ኮንቲኔንታል ነፃ የንግድ ቀጠና) ትግበራን ለመደገፍ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎችን ፣የሎጂስቲክስ ሞዴሎችን እና አዳዲስ የመፍትሄ ማሳያ መንገዶች ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ብሎም በመላው ዓለም የሚከናወኑ የንግድና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ቀልጣፋ፣ አካታች እና ዘላቂ የሚያደርጉ የሎጂስቲክስ መፍትሄዎችን ለማምጣት የኢትዮጵያ ፖስታ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በወርክሾፑ ላይ ተገልጿል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Read More »