የዓለምአቀፍ የፖስታ ህብረት በፖሰታ አባል አገራት መካከል ለሚደረግ የፖስታ መልዕክቶች ልውውጥ የክፍያ ስርዓት በተመለከተ ለስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ሥልጠና ሰጠ፡፡

የዓለምአቀፍ የፖስታ ህብረት በፖሰታ አባል አገራት መካከል ለሚደረግ የፖስታ መልዕክቶች ልውውጥ /UPU Remuneration System/ የክፍያ ስርዓት በተመለከተ ለስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ሥልጠና ሰጠ፡፡

የዓለምአቀፍ ፖስታ ህብረት የክፍያ ስርዓት ኤክስፐርት በሆኑት በሚስተር ፊሊፕ ግሮንዴይን ለአራት ተከታታይ ቀናት ከግንቦት 4- ግንቦት 7/2017 ስልጠናው የተሰጠ ሲሆን በስልጠናው ከተለያዩ ክፍሎች የተውጣጡ ሰላሳ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በአጠቃላይ ስልጠናው የዓለምአቀፍ ፖስታ ህብረት የክፍያ ስርዓት ቴክኒካዊ አሰራር እውቀት ለማሰጨበጥ ያለመ በመሆኑ ከስልጠናው በተገኘው እውቀት መሰረት አሰራራችንን በማሻሻል ረገድ ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚኖሮው ታምኖበታል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »