በኢትዮጵያ ፖስታ እና በቲና ማርት መካከል የጋራ መግባቢያ ሠነድ ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በኦን ላይን የግብይት ስርዓቱ ላይ በአጭር ግዜ ውስጥ ትልቅ ልዩነትን እየፈጠረ ከሚገኘው ቲና ማርት ጋር አብሮ የመስራት ስምምነት ተፈራርሟል።

በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና የ ቲና ማርት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን መካከል የተፈረመው ስምምነት አላማ ደንበኞች በቲና ማርት ድረ-ገፅ እንዲሁም ሞባይል መተግበሪያ ገብተው ለሚያዟቸው የመዋቢያ እቃዎች፣ልብሶች እንዲሁም የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁሶች በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ያሉበት ድረስ ማድረስ ማስቻል መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት በቀለ የኢትዮጵያ ፖስታ ከጀመረው የዲጂታል ገበያ ትግበራ እንዲሁም ካለው የአመታት የሎጅስቲክስ ልምድ አንፃር ይህ ስምምነት ለደንበኞች የሚቀርቡ አገልግሎቶችን በዘመናዊ ሁኔታ ለማሳለጥ የሚያስችለው መሆኑን ተናግረዋል።

የቲና ማርት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን በበኩላቸው ከ131ዓመታት በላይ ልምድ ባለው በኢትዮጵያ ፖስታ በኩል ትእዛዞች የማድረስ ስራውን በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱ ለድርጅታቸው ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን እና ለደንበኞችም ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው እንደሆነ ገልፀዋል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Read More »