News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ሕብረት የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) ጥራት ምዘና ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነ።
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ሕብረት የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) ጥራት ምዘና ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃ ላይ መመደቡ በይፋ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።
በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

አዲስ የተሾሙት የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት በተቋሙ ውስጥ ጉብኝት አድርገዋል፡፡
ባለፉት ሶስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፖስታን ሲያገለግል በቆየው ቦርድ የተተካው አዲሱ ቦርድ አመራር አባላት በተቋሙ ውስጥ በመገኘት በሁሉም የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው ጉብኝት አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።
በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ተከብሯል።
“ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተከብሮ ውሏል።

የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ ቴምብር ተሰራለት፡፡
በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደው የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ያሳተማቸውን ቴምብሮች አስመርቋል፡፡

በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ።
በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ይድነቃቸው ወልደተንሳይ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ፡፡
