News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝት፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንጦጦ በሚገኘው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና የምርምር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።
በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ የ2017 በጀት አመት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2018 በጀት አመት እቅድ ውይይት አካሄደ።
ለሁለት ቀናት በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም በድርጅቱ የስትራቴጂክ ምሰሶዎች ላይ ተመስርቶ የቀረበ ሪፖርት እና የቀጣይ በጀት አመት እቅዶች በስፋት የተቃኙበት ነበር። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ2017 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም የተመዘገበበት እንደሆነ የተነሳ ሲሆን እንደተቋም በቀጣይ ትኩረት ሊሰጥባቸው ይገባል ተብለው በዝርዝር የቀረቡ ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኞች ሰባተኛውን ዙር ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄዱ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኞች ‹‹በመትከል ማንሰራራት›› በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛውን ዙር ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄዱ።