የአለም የፖስታ ቀን ዘንድሮ መስከረም 29 /2017 ለ55ኛ ጊዜ ”ለ150 ዓመታት የዘለቀ ግንኙነት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሕዝቦችን ማጎልበት” በሚል መሪ ቃል በመላው አለም እየተከበረ ይገኛል።
እ.ኤ.አ በ1874 ዓ.ም የተመሠረተው ዓለም አቀፍ የፖስታ ህብረት የተሰኘው ተቋም ምስረታው የተደረገው የሲውዘርላንድ ዋና ከተማ በሆነችው በርን ላይ ነው። ህብረቱ በቁጥር 195 የሚሆኑ አባል አገራት ያሉት ሲሆን ከእነርሱም መካከል ኢትዮጵያ አንዷ በመሆን እ.ኤ.አ.1908ዓ.ም. ተቀላቅላለች። ዓለም አቀፍ የፖስታ ህብረት ከተመሰረተ 150ኛ ዓመቱን ከአለም የፖስታ ቀን ጋር ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ ቀን በማክበር ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ ይህንን ታላቅ ቀን በአለም ዙሪያ ካሉ ወገኖቻችን እና ከእኛ ጋር ለማክበር ትውልድ የተሻገረ የወዳጅነት ታሪክን ይጎብኙ።
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡











