የአለም የፖስታ ቀን አከባበር በየኢትዮጵያ ፖስታ

የአለም የፖስታ ቀን ዘንድሮ መስከረም 29 /2017 ለ55ኛ ጊዜ ”ለ150 ዓመታት የዘለቀ ግንኙነት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሕዝቦችን ማጎልበት” በሚል መሪ ቃል በመላው አለም እየተከበረ ይገኛል።
እ.ኤ.አ በ1874 ዓ.ም የተመሠረተው ዓለም አቀፍ የፖስታ ህብረት የተሰኘው ተቋም ምስረታው የተደረገው የሲውዘርላንድ ዋና ከተማ በሆነችው በርን ላይ ነው። ህብረቱ በቁጥር 195 የሚሆኑ አባል አገራት ያሉት ሲሆን ከእነርሱም መካከል ኢትዮጵያ አንዷ በመሆን እ.ኤ.አ.1908ዓ.ም. ተቀላቅላለች። ዓለም አቀፍ የፖስታ ህብረት ከተመሰረተ 150ኛ ዓመቱን ከአለም የፖስታ ቀን ጋር ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ ቀን በማክበር ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ ይህንን ታላቅ ቀን በአለም ዙሪያ ካሉ ወገኖቻችን እና ከእኛ ጋር ለማክበር ትውልድ የተሻገረ የወዳጅነት ታሪክን ይጎብኙ።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »