የአለም የፖስታ ቀን ዘንድሮ መስከረም 29 /2017 ለ55ኛ ጊዜ ”ለ150 ዓመታት የዘለቀ ግንኙነት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሕዝቦችን ማጎልበት” በሚል መሪ ቃል በመላው አለም እየተከበረ ይገኛል።
እ.ኤ.አ በ1874 ዓ.ም የተመሠረተው ዓለም አቀፍ የፖስታ ህብረት የተሰኘው ተቋም ምስረታው የተደረገው የሲውዘርላንድ ዋና ከተማ በሆነችው በርን ላይ ነው። ህብረቱ በቁጥር 195 የሚሆኑ አባል አገራት ያሉት ሲሆን ከእነርሱም መካከል ኢትዮጵያ አንዷ በመሆን እ.ኤ.አ.1908ዓ.ም. ተቀላቅላለች። ዓለም አቀፍ የፖስታ ህብረት ከተመሰረተ 150ኛ ዓመቱን ከአለም የፖስታ ቀን ጋር ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ ቀን በማክበር ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ ይህንን ታላቅ ቀን በአለም ዙሪያ ካሉ ወገኖቻችን እና ከእኛ ጋር ለማክበር ትውልድ የተሻገረ የወዳጅነት ታሪክን ይጎብኙ።

News
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።
የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።











