News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዕቅድ ውይይቱ አጠናቀቀ፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዕቅድ ውይይቱ አጠናቀቀ፡፡
ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት 3.85 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰብስቧል። ይህ አፈጻጸም ከባለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ30 በመቶ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፣ ተቋሙ በሌሎች ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎችም አመርቂ ውጤት ያስመዘገበበት ስኬታማ ዓመት ሆኖ አልፏል።

አዲስ የተሾሙት የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት በተቋሙ ውስጥ ጉብኝት አድርገዋል፡፡
ባለፉት ሶስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፖስታን ሲያገለግል በቆየው ቦርድ የተተካው አዲሱ ቦርድ አመራር አባላት በተቋሙ ውስጥ በመገኘት በሁሉም የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው ጉብኝት አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።
በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ተከብሯል።
“ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተከብሮ ውሏል።

የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ ቴምብር ተሰራለት፡፡
በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደው የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ያሳተማቸውን ቴምብሮች አስመርቋል፡፡

በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ።
በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ይድነቃቸው ወልደተንሳይ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መልእክት።
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልእክታቸው ላይ የግድቡ መጠናቀቅ እንደ ሃገር
