የዓለም ባንክ እና የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በየኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት አካሄዱ።

የአለም ባንክ እና የፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ካርዶችን በማተም እና በማሰራጨት ላይ ያለውን የሥራ ሂደት እንዲሁም የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥን በየኢትዮጵያ ፖስታ በመገኘት ተመልክተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ዜጎች ከየኢትዮጵያ ፖስታ ጋር እንዴት እንደሚገናኙ ከመጀመሪያው የካርድ ህትመት ጥያቄ እስከ መጨረሻ ካርድ አሰባሰብ ድረስ የደንበኞችን ጉዞ ምን እንደሚመስል ቃኝተዋል።

በተጨማሪም ለዜጎች የፋይዳ አገልግሎት ተደራሽነትን ከማስፋፋት አንፃር የኢትዮጵያ ፖስታ አጋርነትን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር የመገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቢረዳ እንዲሁም የንብረት አስተዳደር ክፍል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ይፍቱስራ መኮንን መገልገያ ቁሳቁሶቹን ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያስረከቡ ሲሆን የመቄዶኒያ አረጋዉያን የቡራኬ ስነስርዓት አድርገዋል።

Read More »
News

የ2024 የእስያ ፊላቴሊክ ኤግዚቢሽን በቻይና።

በሻንጋይ የተካሄደው የ2024 የኤዥያ አለም አቀፍ የቴምብር ኤግዚቢሽን የእስያን ባህል በፊላቴሊ ጥበብ የሚያሳይ ደማቅ በዓል ነበር። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች አስደናቂውን የቴምብር ማሳያ አድንቀዋል፣ እያንዳንዱም የቴምብር ስራዎች ታሪክን፣ ጥበብን እና ወግን ይናገራሉ።

Read More »
News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »