የሩሲያው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት አደረገ።

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስተባባሪነት መቀመጫውን ሩሲያ ላይ ያደረገው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ተገኝተው ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

የ RWB ልኡካን ቡድን የኢትዮጵያ ፖስታ ሲደርስ በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በከፍተኛ አመራር ቡድኑ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

በውይይቱ ላይም አለም ዓቀፍ የኢ-ኮሜርስ ንግዱ ላይ ሁለቱ አጋር ድርጅቶች በጋራ ሊሰሩባቸው ስለሚችሉ ነጥቦች በማንሳት ጥልቅ ውይይት አድርገዋል፡፡

ከውይይቱም ባሻገር የልኡካን ቡድኑ አባላት በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራአስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በከፍተኛ አመራር ቡድኑ አማካኝነት የተለያዩ የኢትዮጵያ ፖስታን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች የሥራ ሁኔታ እንዲሁም የኢ-ኮሜርስ መጋዘኖችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱም ወቅት ጎብኚዎቹ በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ የተመለከቱት የአሠራረር ሁኔታ ከጠበቁት በላይ እንደሆነ እና ደስ እንደተሰኙበት ተናግረው በቀጣይ በጋራ ሊሠሩባቸው የሚችሉባቸውን መንገዶች ማመቻቸት እና ወደሥራው መግባት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »