የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝት፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንጦጦ በሚገኘው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና የምርምር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በማዕከሉ ጉብኝታቸው ወቅት ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና ወደፊት የሳተላይት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሊሰሩ በታቀዱት ስራዎች ላይ ትልቅ እምነት እና ተስፋ እንዳሳደሩም ገልፀዋል።

በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም እንዲሁ በማዕከሉ ጉብኝታቸው መደሰታቸውን ገልጸው ለነገዋ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ መሠረትነት ጉልህ ሚና የሚጫወት ተቋም በመጎብኘታቸው እና በሥራ አጋርነት አብረው መስራት በመቻላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሀይ ለተጋባዥ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በጉብኝቱም ወቅት በማዕከሉ ስለሚከናወኑ የምርምር ተግባራትና የሳተላይት መረጃዎችን በመሰብሰብ ለተለያዩ አካላት መረጃዎችን በመስጠት እያበረከተ ስላለው አስተዋፆኦ በዝርዝር ገለጻ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ የሚታወስ ነው።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Read More »