የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝት፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንጦጦ በሚገኘው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና የምርምር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በማዕከሉ ጉብኝታቸው ወቅት ባዩት ነገር መደነቃቸውን እና ወደፊት የሳተላይት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሊሰሩ በታቀዱት ስራዎች ላይ ትልቅ እምነት እና ተስፋ እንዳሳደሩም ገልፀዋል።

በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም እንዲሁ በማዕከሉ ጉብኝታቸው መደሰታቸውን ገልጸው ለነገዋ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ መሠረትነት ጉልህ ሚና የሚጫወት ተቋም በመጎብኘታቸው እና በሥራ አጋርነት አብረው መስራት በመቻላቸው ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ፀሀይ ለተጋባዥ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በጉብኝቱም ወቅት በማዕከሉ ስለሚከናወኑ የምርምር ተግባራትና የሳተላይት መረጃዎችን በመሰብሰብ ለተለያዩ አካላት መረጃዎችን በመስጠት እያበረከተ ስላለው አስተዋፆኦ በዝርዝር ገለጻ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ የሚታወስ ነው።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »