በኢትዮጵያ ፖስታ እና በኢግልድ የሸቀጦች ጅምላ ንግድ አስመጪ ድርጅት መካከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ::

በኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና በኢግልድ የኢንዱስትሪ ዉጤቶች ግዥ እና ሽያጭ ዘርፍ ም/ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባዬ ገዛኸኝ የተፈረመው ይህ አጋርነት የኢግልድ የኢንዱስትሪ ዉጤቶችን በኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፍ ፖስታ ቤቶች በኩል ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግና በኦንላይን የኢግልድን የኢንዱስትሪ ዉጤቶች ለሚገበያዩ ደንበኞች በሚመርጡት ቦታ ዕቃዎችን ለማድረስ የሚያስችል ነው::
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፖስታ ተደራሽነቱን ከማስፋት አንፃር የኢግልድን ቅርንጫፍ ቢሮዎች ለሚሰጣቸዉ የተለያዩ አገልግሎቶች በፍራንቻይዝነት መጠቀምን ያካትታል ::

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Read More »