በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በኢስት አፍሪካ ትሬዲንግ ሃውስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኤልያብ ጌታቸው የተፈረመው ይህ የአጋርነት ሰነድ የቤት ለቤት መልእክቶችን እና ሌሎች የመልዕክት ልውውጥ አገልግሎቶችን ለደንበኞች ለማድረስ የሚያስችል ነው። የኢትዮጵያ ፖስታ ባሉት 700 የሃገር ውስጥ ቅርንጫፍ ፖስታ ቤቶች የበሽ ገበያ እንዲሁም በትልቅ የሎጅስቲክስ አቅም የሚጓጓዙ የኢስት አፍሪካ ትሬዲንግ ሃውስ ምርቶችን በሃገር ውስጥ እንዲሁም በተለያዩ የውጪ ሃገራት ለሚገኙ ደንበኞች ማድረስን ያካትታል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ለመቄዶኒያ አበረከተ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት አንድ አካል አድርጎ በተለያዩ ዙሮች ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡









