የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኦሮሚያ ጤና ቢሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ።

የኢትዮጵያ ፖስታ  ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመገናኘት በክልሉ የሚገኙ የጤና ናሙና ሎጂስቲክስ፣ የፋይናንሺያል እና የመልዕክት አገልግሎቶችን በቅንጅት መስጠት ላይ ያተኮረ የትብብር ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሂዷል። የኢትዮጵያ ፖስታ ላለፉት አስር አመታት ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በመላ ሀገሪቱ ከሚገኙ የመንግስት የጤና ተቋማት የጤና ናሙናዎችን ተቀብሎ ወደ መመርመሪያ ጣቢያዎች በማድረስና ውጤቱንም መልሶ ለጤና ተቋማት በማስረከብ የሎጅስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ይህ አሰራር በናሙና ዝውውር ላይ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ለህብረተሰቡ የጤና ሽፋንን ከመጨመር አንፃር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል።

በኦሮሚያ ጤና ቢሮ ስር ከሚገኙ የዞንና ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊዎች ጋር  የተደረገው ይህ ውይይት የጤና ናሙና ሎጂስቲክስን በቴክኖሎጂ ማዘመንና አጋርነትን ከፍ በማድረግ ለህብረተሰቡ ይበልጥ ተደራሽ መሆን ላይ ያተኮረ ነበር። ይህንንም ለመተግበር የኢትዮጵያ ፖስታ በኦሮሚያ ጤና ቢሮ ሥር በሚገኙ 1440 የጤና ተቋማት ውስጥ የአገልግሎት መስጫ ቦታዎችን ለማግኘት የሚያስችል ስምምነት ላይ ተደርሷል። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ  የኢትዮጵያ ፖስታ የናሙና አሰባሰብ ሂደቱን ለማቀላጠፍ እና ለአካባቢው ማህበረሰብ ተጨማሪ አገልግሎቶችን ለመስጠት ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በነዚህ የጤና ተቋማት ውስጥ አገልግሎት መስጫ ጽ/ቤቶችን በማቋቋም አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።

More updates Ethiopost

News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኦሮሚያ ጤና ቢሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ።

የኢትዮጵያ ፖስታ  ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመገናኘት በክልሉ የሚገኙ የጤና ናሙና ሎጂስቲክስ፣ የፋይናንሺያል እና የመልዕክት አገልግሎቶችን በቅንጅት መስጠት ላይ ያተኮረ የትብብር ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሂዷል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በኢስት አፍሪካ ትሬዲንግ ሃውስ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ::

በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በኢስት አፍሪካ ትሬዲንግ ሃውስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኤልያብ ጌታቸው የተፈረመው ይህ የአጋርነት ሰነድ የቤት ለቤት መልእክቶችን እና ሌሎች የመልዕክት ልውውጥ አገልግሎቶችን ለደንበኞች ለማድረስ የሚያስችል ነው።

Read More »
News

በየኢትዮጵያ ፖስታ እና በኦሮምያ ባንክ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ ::

በየኢትዮጵያ ፖስታ ኮሜርሺያል ቺፍ ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና በኦሮምያ ባንክ የሪቴል እና ኤስ ኤም ኢ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ጆቴ ቀናቴ የተፈረመው ይህ አጋርነት ከ700 በላይ ቅርንጫፎች ባሉት የኢትዮጵያ ፖስታ የባንክ አገልግሎቶችን በወኪልነት እንዲሰራ የሚያስችል ነው።

Read More »