የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

በ 1967 ዓ.ም የተቋቋመው ታሪካዊው የፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመቱን በዛሬው እለት በድምቀት አክብሮ ውሏል፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች እና ታላላቅ የሃገራችን ሰአሊያን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም በፖስታ ሙዚየሙ ላይ ሊሠሩ ከታቀዱት የማስፋፊያ ሥራዎች አኳያ የባለድርሻ አካላቱ ሃሳብ እና እገዛ እንደሚያስፈልግ እና በብዙ መልኩ ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ መሆኑንም ጠቅሰው ለታዳሚው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የፖስታ ሙዚየሙ ሱፐርቫይዘር የሆኑት አቶ ደረጀ ብርሃኑ ለተሳታፊዎቹ በሙዚየሙ ውስጥ ያሉትን 50 ዓመታትን ያስቆጠሩ የቴምብር ሥራዎችን አስጎብኝተው በቅርቡ በካታሎግ መልክ ተዘጋጅተው ለጎብኚዎች እንዲደርሱ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዚሁ ክብረ በዓል ላይ የተገኙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ማለትም አቶ አሰፋ ጉያ፣ የሰዓሊ ቦጋለ በላቸው ቤተሰቦች እንዲሁም ሌሎች አንጋፍ አርቲስቶች በመድረኩ ላይ የፖስታ ሙዚየሙ አሁን ላለበት ደረጃ መድረስ በየደረጃው ያሉ የኢትዮጵያ ፖስታ የስራ መሪዎችን አመስግነው ሙዚየሙን ለማዘመን እና ለማስፋፋት በሚደረገው ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ከኢትዮጵያ ፖስታ ጎን በመቆም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል፡፡

በመጨረሻም የፖስታ ሙዚየሙ የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል በቀጣይም ለአንድ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ እንደሚቀጥል እና ጎብኚዎችም መጥተው እየጎበኙ የዚህ ታሪክ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል፡፡

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Read More »