ላለፉት ሶስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፖስታን ሲያገለግል የነበረው ቦርድ አመራሮች እና አባላት የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በታላቅ ክብር ሽኝት ተደርጎላቸዋል።
በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።
እንዲሁም በዚሁ እለት አዲሱ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት በእለቱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በተያያዘም በመድረኩ ላይ የቀድሞው የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መስፍን ጣሰው የቦርድ ሰብሳቢነትን ቦታ ለፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የቀድሞ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ክብርት ወ/ሮ ሐና አርአያስላሴ ቦታውን አስረክበዋል።














