22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ተከብሯል።

“ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተከብሮ ውሏል።

በእለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በቦታው ተገኝተው ለመላው የዝግጅቱ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው አያይዘውም በተቋሙ ውስጥ ያለ ሁሉም ሠራተኛ የሙስና ተጋላጭነትን በመከላከል እና ብልሹ አሠራሮች ሲታዩ በፍጥነት የእርምት እርምጃዎችን በመውሰድ ተቋማዊ እና ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣ አሳስበዋል።በመቀጠልም ከእለቱ ጋር በተያያዘ የተዘጋጀው ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል።

በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት በቀለ 22ኛውን የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በማስመልከት የተዘጋጀውን ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቡ ሲሆን በተሳታፊዎች መካከልም የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል።

በመጨረሻም በእለቱ የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሀብት ምዝገባ የተከናወነ ሲሆን በአርአያነት ይህንን ተግባር በመከወናቸው ታላቅ ምስጋና በማቅረብ የዝግጅቱ ፍፃሜ ሆኗል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »