የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የመታሰቢያ ቴምብሮቹንም የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በጋራ በመሆን ይፋ አድርገዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አንጋፋው የኢትዮጵያ ፖስታ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ታሪኮች በተለያዩ ጊዜያት በቴምብር ሥራዎች እየቀረጸ ሲያስቀምጥ የኖረ ተቋም እንደሆነ ገልጸው ዩኒቨርሲቲያቸውም ከኢትዮጵያ ፖስታ ጋር በመስራቱ ኩራት እና ደስታ እንደሚሰማው ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም የተቋማትን የዘመናት አበርክቶት ለአለም በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ያለው እና የሚገኘው የኢትዮጵያ ፖስታ ሌሎች ዝግጅታቸው የተጠናቀቁ የተቋማት ቴምብሮችን ከተቋማቱ ጋር በመሆን በየጊዜው ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚያደርግ እና አሁንም ይህንኑ አገልግሎት ለሚሹ ተቋማት በሩ ክፍት እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »