የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በይፋ አስመረቀ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመረቀ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ያበለጸጋቸውን የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመርቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ለ132 ዓመታት የቆየውን የታማኝነት አገልግሎቱን ከዘመናዊው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት፣ “ሳጥን አልባ (Virtual)” የመልዕክት አገልግሎት እና “የፖስታ ገበያ” የኢ-ኮሜርስ መተግበሪያዎችን በስካይላይት ሆቴል በደመቀ ሁኔታ አስመርቋል። ይህ ታሪካዊ እመርታ ተቋሙ ከመቶ ዓመታት በላይ እየሰራበት የነበረውን ልምድ ከዘመኑ የፈጠራ ስራዎች ጋር በማዋሃድ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ መፍትሄዎችን ለደንበኞቹ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት ነው።

አዲሱ የቨርቹዋል ፖስታ ሳጥን አገልግሎት የደንበኞችን የሞባይል ስልክ ቁጥር እንደ ዲጂታል አድራሻ እንዲያገለግል የሚያደርግ ሲሆን፣ ይህም ደንበኞች ከየትኛውም የዓለም ክፍል የሚላኩላቸውን መልዕክቶች እና ጥቅሎች በስልካቸው በሚደርሳቸው ፈጣን ማሳወቂያ መከታተል እንዲችሉና ባሉበት ቦታ ሆነው በቤት ለቤት አገልግሎት እንዲረከቡ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።

በማስጀመሪያ ስነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ሚኒስትር ክቡር አቶ መላኩ አለበል፣ እነዚህ መድረኮች የ”ዲጂታል ኢትዮጵያ” ስትራቴጂን ወደ ተግባራዊ መፍትሄ የለወጡ ትልቅ ስኬቶች መሆናቸውን ገልጸው፤ በተለይም የፖስታ ገበያ (postGebeya) መተግበሪያ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚገጥሟቸውን የንግድ እንቅፋቶችን በመቀነስ ምርቶቻቸውን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲያስተዋውቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትልቅ ዕድል እንደሚከፍት አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ፤ ተቋሙ በዲጂታል ዘመን ደንበኞችን ከገበያው ጋር ይበልጥ የሚያቀራርብ አዲስ አወቃቀር መከተሉን ገልጸው፣ አዲሱ አሰራር የደንበኞችን ምቾትና እርካታ ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር አረጋግጠዋል። በአጠቃላይ ይህ ጅማሬ የኢትዮጵያን የዘመናዊነት ጉዞ የሚያንፀባርቅና በሀገር ውስጥ የሚላኩ ዶክመንቶችንም ሆነ ጥቅል መልዕክቶችን በቴክኖሎጂ የታገዘና የተሳለጠ እንዲሆኑ የሚያደርግ ግዙፍ እርምጃ ነው።

በስነስርአቱ ላይ የተገኙ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶችም ይህ የፖስታ ገበያ መተግበሪያ መፈጠሩ ምርቶቻቸውን በመላው ዓለም ለሚገኙ ደንበኞች እንዲያደርሱ እና በግብይት ልምዳቸውም በብዙ መልኩ ከፍ ያለ ለውጥ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »