በኢትዮጵያ ፖስታ እና በኢግልድ የሸቀጦች ጅምላ ንግድ አስመጪ ድርጅት መካከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ::

በኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና በኢግልድ የኢንዱስትሪ ዉጤቶች ግዥ እና ሽያጭ ዘርፍ ም/ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አበባዬ ገዛኸኝ የተፈረመው ይህ አጋርነት የኢግልድ የኢንዱስትሪ ዉጤቶችን በኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፍ ፖስታ ቤቶች በኩል ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግና በኦንላይን የኢግልድን የኢንዱስትሪ ዉጤቶች ለሚገበያዩ ደንበኞች በሚመርጡት ቦታ ዕቃዎችን ለማድረስ የሚያስችል ነው::
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፖስታ ተደራሽነቱን ከማስፋት አንፃር የኢግልድን ቅርንጫፍ ቢሮዎች ለሚሰጣቸዉ የተለያዩ አገልግሎቶች በፍራንቻይዝነት መጠቀምን ያካትታል ::

More updates Ethiopost

News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኦሮሚያ ጤና ቢሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ላይ ያተኮረ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ።

የኢትዮጵያ ፖስታ  ከኦሮሚያ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመገናኘት በክልሉ የሚገኙ የጤና ናሙና ሎጂስቲክስ፣ የፋይናንሺያል እና የመልዕክት አገልግሎቶችን በቅንጅት መስጠት ላይ ያተኮረ የትብብር ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሂዷል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በኢስት አፍሪካ ትሬዲንግ ሃውስ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ::

በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በኢስት አፍሪካ ትሬዲንግ ሃውስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኤልያብ ጌታቸው የተፈረመው ይህ የአጋርነት ሰነድ የቤት ለቤት መልእክቶችን እና ሌሎች የመልዕክት ልውውጥ አገልግሎቶችን ለደንበኞች ለማድረስ የሚያስችል ነው።

Read More »
News

በየኢትዮጵያ ፖስታ እና በኦሮምያ ባንክ መካከል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ ::

በየኢትዮጵያ ፖስታ ኮሜርሺያል ቺፍ ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና በኦሮምያ ባንክ የሪቴል እና ኤስ ኤም ኢ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ጆቴ ቀናቴ የተፈረመው ይህ አጋርነት ከ700 በላይ ቅርንጫፎች ባሉት የኢትዮጵያ ፖስታ የባንክ አገልግሎቶችን በወኪልነት እንዲሰራ የሚያስችል ነው።

Read More »