News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ – የሰራተኞች ህብረት ቀን በድምቀት ተከበረ።
የኢትዮጵያ ፖስታ የሰራተኞች ህብረት ቀን ላይ ከዋና መስሪያ ቤት እንዲሁም ከሁሉም የዲስትሪክት ቅርንጫፍ የተወጣጡ ሃላፊዎች እና ሰራተኞች ከጥር 24 እስከ ጥር 25፣ 2017 ዓ.ም ሱሉልታ በሚገኘው በያያ ቪሌጅ በድምቀት አክብሯል።

የአለም የፖስታ ቀን አከባበር በየኢትዮጵያ ፖስታ
የአለም የፖስታ ቀን ዘንድሮ መስከረም 29 /2017 ለ55ኛ ጊዜ ”ለ150 ዓመታት የዘለቀ ግንኙነት እና በአለም ዙሪያ ያሉ ሕዝቦችን ማጎልበት” በሚል መሪ ቃል በመላው አለም እየተከበረ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፖስታ የስራ ላይ ልምምድ ሲያደርጉ ለነበሩ አዲስ ተመራቂ ተማሪዎች በሰርተፊኬት እውቅና ሰቷል።
በፋይናንስ፣ በሰው ሃይል አስተዳደር፣ በደንበኛ አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች የስራ ክፍሎች ውስጥ ተመድበው ሲሠሩ የነበሩ ተማሪዎችን ለ 2 ወራት በቆየ የስራ ላይ ልምምድ በማሰማራት ስለ ስራው በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አድርጓል።

የኢትዮጵያ ፖስታ የ2017 ዓ.ም የዓዲስ ዓመት ዋዜማን በዋናው መስሪያ በደመቀ ሁኔታ አክብሯል።
ይህ ማዕድ በመጋራት፣ በአብሮነት፣ በሚፍለቀለቁ ሳቆች እና በውድ ጊዜዎች የተሞላው የአዲስ አመት ዋዜማ አከባበር መጪው ዘመን በስኬት የተሞላ ይሆን ዘንድ በህብረት እና በትጋት የመስራት አስፈላጊነትንም የሚያሳይ ነበር።

የኢትዮጵያ ፖስታ የ 2016 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እና የ2017 ዓ.ም እቅድ ላይ ሠራተኞቹ ጋር ውይይት አድርጓል።
የኢትዮጵያ ፖስታ የ 2016 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እና የ2017 ዓ.ም እቅድ ላይ በተለያዩ ሀገሪቱ ክፍሎች ከሚገኙ ሠራተኞቹ ጋር ውይይት አድርጓል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከአለም አቀፉ የኢ-ኮሜርስ ድርጅት አሊባባ ጋር ውይይት አካሂዷል።
የኢትዮጵያ ፖስታ ከአለም አቀፉ የኢ-ኮሜርስ ድርጅት አሊባባ ጋር ስትራቴጅካዊ በሎጂስቲክስ ዘርፍ አብሮ ለመስራት ያለመ ውይይት አካሂዷል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኞች የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ችግኝ በመትከል እና በመንከባከብ የሀገሪቱን መጪ ጊዜ የተሻለ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ ይገኛል።