በዛሬው ዕለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ጉብኝት እና ውይይት አደረጉ። ውይይቱ በዋነኝነት የኢትዮጵያ ፖስታ አሁን ያለበትን ደረጃ ካለው ሰራተኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሃላፊዎች ድረስ ያለውን እይታ የቃኘ ነበር። በተጨማሪም ከጉብኝቱ እንደተገነዘቡት የኢትዮጵያ ፖስታ በሁሉም መስክ በሚባል ደረጃ አመርቂ ለውጥ እያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ከሰራተኛው በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ከሃላፊዎች ማብራርያ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ በደንበኞች አገልግሎት ጥራት ተሸላሚ ሆነ።
የአለም አቀፉ የፖስታ ህብረት 28ኛው ጠቅላላ ጉባዬ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ባሳየው የላቀ አፈፃፀም የ2024 የፈጣን መልእክት የደንበኞች አገልግሎት ጥራት ሽልማትን ተቀብሏል።













