የኢትዮጵያ ፖስታ 131ኛ ዓመት የምስረታ በዓል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ላለፉት 131 ዓመታት በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ግንባር ቀደም የግንኙነት ምሰሶ በመሆን ሰዎችን ከሰዎች ተቋማትን ከተቋማት በማገናኘት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ባህላዊ ትስስር እንዲጠነክርና የንግድ ልውውጥ እንዲያድግ የበኩሉን አስተዋፅዖ ሲያበረክት የቆየ አንጋፋ የህዝብ ተቋም ነው።

በቀድሞ ጊዜ ከነበረው የፖስታ ልውውጥ አሰራር አንስቶ እስከ አሁኑ ዘመናዊ የሎጂስቲክስና የዲጂታል ዘመን ከሁኔታዎችና ወቅታዊ ፍላጐቶች ጋር እራሱን በማስተዋወቅና በማዘመን እንዲሁም የአገልግሎት አድማሱንና ተደራሽነቱን በማስፋት ላለፉት አንድ መቶ ሠላሣ አንድ ዓመታት በትጋትና በአገልጋይነት መንፈስ ተጉዟል።

ዛሬም ይህን ትውልዶች የተቀባበሉትን አስደናቂ ምዕራፍ 131ኛ የምስረታ በዓል ስናከብር የዚህ ጉዞ አካል የሆኑትን ውድ ሰራተኞቻችንን፣ ውድ ደንበኞቻችንን እና አጋሮቻችንን በማመስገንና ላበረከቱት አስተዋፅዖ እውቅና በመስጠት ነው።

በቀጣይም አኩሪ የሕዝብ አገልጋይነት ታሪካችንን ሰንቀን ያሁኑንና ቀጣዩን ትውልድ ለማገልገል ይረዳን ዘንድ ቴክኖሎጂን በማቀፍ፣ አዳዲስ የአሰራር ስልቶችን በመንደፍና የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል በማድረግ ሁሌም ከትናንቱ በተሻለ ልናገለግልዎ ዝግጁ መሆናችንን በመግለጽ ነው።

መልካም 131ኛ ዓመት!

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »