በትናንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከፍተኛ የስራ አመራሮች በዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ እና በምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ኃ/ሚካኤል የተመራ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ልዑክ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤትን የጎበኙ ሲሆን በድርጅቱ የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ላይ ስትራቴጂካዊ ውይይት አድርገዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ባደረጉት የስድስት ወር የስራ አፈጻጸም ገለፃ ላይ ቁልፍ ስኬቶችን፣ ተግዳሮቶችን እና የወደፊት የእድገት እቅዶችን ያቀረቡ ሲሆን ገለጻውን ተከትሎ አገልግሎቶችን ማዘመን፣ ማስፋፋት እና ፈጠራን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል። በቀጣይም የትኩረት እና ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በኩል ተሰጥቷል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።
ይህ ስምምነት 700 በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፎች የሰነዶችን ምዝገባ አገልግሎትን እንዲያካሄድ የሚስችላቸው ነው።