በትናንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከፍተኛ የስራ አመራሮች በዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ እና በምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ኃ/ሚካኤል የተመራ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ልዑክ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤትን የጎበኙ ሲሆን በድርጅቱ የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ላይ ስትራቴጂካዊ ውይይት አድርገዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ባደረጉት የስድስት ወር የስራ አፈጻጸም ገለፃ ላይ ቁልፍ ስኬቶችን፣ ተግዳሮቶችን እና የወደፊት የእድገት እቅዶችን ያቀረቡ ሲሆን ገለጻውን ተከትሎ አገልግሎቶችን ማዘመን፣ ማስፋፋት እና ፈጠራን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል። በቀጣይም የትኩረት እና ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በኩል ተሰጥቷል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ለመቄዶኒያ አበረከተ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት አንድ አካል አድርጎ በተለያዩ ዙሮች ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡













