22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ተከብሯል።

“ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተከብሮ ውሏል።

በእለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በቦታው ተገኝተው ለመላው የዝግጅቱ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው አያይዘውም በተቋሙ ውስጥ ያለ ሁሉም ሠራተኛ የሙስና ተጋላጭነትን በመከላከል እና ብልሹ አሠራሮች ሲታዩ በፍጥነት የእርምት እርምጃዎችን በመውሰድ ተቋማዊ እና ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣ አሳስበዋል።በመቀጠልም ከእለቱ ጋር በተያያዘ የተዘጋጀው ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል።

በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት በቀለ 22ኛውን የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በማስመልከት የተዘጋጀውን ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቡ ሲሆን በተሳታፊዎች መካከልም የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል።

በመጨረሻም በእለቱ የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሀብት ምዝገባ የተከናወነ ሲሆን በአርአያነት ይህንን ተግባር በመከወናቸው ታላቅ ምስጋና በማቅረብ የዝግጅቱ ፍፃሜ ሆኗል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »