“ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ቃል 22ኛው የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች እና ሠራተኞች በተገኙበት ተከብሮ ውሏል።
በእለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በቦታው ተገኝተው ለመላው የዝግጅቱ ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው አያይዘውም በተቋሙ ውስጥ ያለ ሁሉም ሠራተኛ የሙስና ተጋላጭነትን በመከላከል እና ብልሹ አሠራሮች ሲታዩ በፍጥነት የእርምት እርምጃዎችን በመውሰድ ተቋማዊ እና ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣ አሳስበዋል።በመቀጠልም ከእለቱ ጋር በተያያዘ የተዘጋጀው ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል።
በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትእግስት በቀለ 22ኛውን የዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በማስመልከት የተዘጋጀውን ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ ያቀረቡ ሲሆን በተሳታፊዎች መካከልም የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል።
በመጨረሻም በእለቱ የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ሀብት ምዝገባ የተከናወነ ሲሆን በአርአያነት ይህንን ተግባር በመከወናቸው ታላቅ ምስጋና በማቅረብ የዝግጅቱ ፍፃሜ ሆኗል።













