የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ ቴምብር ተሰራለት፡፡

በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደው የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ያሳተማቸውን ቴምብሮች አስመርቋል፡፡

በዝግጅቱ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ እና ዲፕሎማት ዶ/ር ተቀዳ ዓለሙ ፣የቀድሞ የትምህርት ሚኒስቴር ዶ/ር ያየህይራድ ቅጣው፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የካፍ ሥራ አስፈጻሚ እና የፊፋ ጸረ-ዘረኝነትና ጸረ-አግላይነት ኮሚቴ አባል አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የኢ/እ/ፌ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን፣ የመንግሥቱ ወርቁ መታሰብያ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰሎሞን በቀለ፣ የመጽሐፉ ጸሐፊ ዶ/ር ሰሎሞን በርኼ፣ የቀድሞ ተጫዋች፣ የኮሚቴ አባላት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የመገናኛ ብዙሀን አካላት በተገኙበት የቴምብር ስራዎች እንዲሁም በስፖርተኛው ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ተመርቋል፡፡

በተያያዘም የኢትዮጵያ ፖስታ ከቴምብር ሥራዎች ጀምሮ ለዝግጅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ዋንጫ የተበረከተለት ሲሆን ከመድረኩም ታላቅ ምስጋና ተችሮታል፡፡

በመጨረሻም የታላቁ የእግር ኳስ ሰው የመንግሥቱ ወርቁን ቤተሰብ በመወከል ንግግር ያደረጉት ፓስተር እሸቴ በቀለ እንደ አጠቃላይ የትኢዮጵያ ፖስታን ጨምሮ ታላላቅ የሀገር ባለውለታዎች እና ባለአደራዎች ይህን መርሐ ግብር በማዘጋጀታቸው በቤተሰብ ስም በማመስገን ስለ መንግሥቱ ወርቁ በስንኝ የታጀበ ምስክርነት አቅርበዋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »