በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ።

በጉብኝቱ ወቅት የኢትዮጵያ ፖስታ ለኢ-ኮሜርስ ሥራ እያደረገ ያለውን ዝግጁነት እና የተለያዩ የሥራ ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በቅርቡ ወደ ሥራ የሚገባውን የኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ ጨምሮ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎቱን በተሻለ ለማዘመን እየሰራቸው ባሉ ሥራዎች ዙሪያ በዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በድርጅቱ አመራሮች ለኮሚቴው ገለጻ ተደርጓል፡፡

በተመሳሳይ በውይይቱ ላይም የኢትዮጵያ ፖስታ ኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ የአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽ ለማድረግ ያለመ እና የንግድ ስርዓቱንም በማዘመን ሂደት ትልቅ አወንታዊ ሚና እንደሚኖረው የተነሳ ሲሆን፤ ኮሚቴው አጠቃላይ የንግድ ምህዳሩን ለኢ-ኮሜርስ ምቹ ከማድረግ አንጻር መሰራት በሚገባቸው ሥራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በመጨረሻም በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ይድነቃቸው ወልደተንሳይ እንዲሁም የኮሚቴው አባላት በጉብኝታቸው የተመለከቱት የኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ሥራ ዝግጅት አበረታች መሆኑን ገልጸው ተጠናክሮ መቀጠልና በሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎችም በተመሳሳይ ዝግጅት መደረግ እንዳለበት አንስተዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »