🎉🎉🎉እንኳን ደስ አለን!🎉🎉🎉
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ሕብረት የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) ጥራት ምዘና ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃ ላይ መመደቡ በይፋ ተገልጿል።
ይህ ክብር የኢትዮጵያ ፖስታ በዘመናዊ የፖስታ አገልግሎት፣ በፈጣን ሎጂስቲክስ አቅርቦት እና በደንበኛ ተኮር የአገልግሎት ጥራት ላይ ያደረገውን ተከታታይ ማሻሻያ የሚያሳይ ሲሆን፣ ድርጅቱ በአፍሪካ እና በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ የፖስታ አገልግሎት ተቋም እየሆነ መምጣቱን ያረጋግጣል።
ይህ ውጤት የኢትዮጵያ ፖስታ ሠራተኞች ትጋት፣ የአመራሮች ቁርጠኝነት ድምር ውጤት በመሆኑ ለሁሉም የተቋሙ ማሕበረሰብ ታላቅ ምስጋና ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ወደፊትም ዘመናዊ፣ አስተማማኝ እና ደንበኛ ተኮር አገልግሎት በማቅረብ በሀገራችን የሎጂስቲክስና የፖስታ ዘርፍ ልማት ውስጥ ያለውን ሚና በቀጣይነት ያጠናክራል።





