የኢትዮጵያ ፖስታ የሰራተኞች ቀን በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሰራተኞችን ትጋት፣ ቁርጠኝነትና ስኬት ለማክበር እና ለማጠናከር ያዘጋጀው ዓመታዊ የሰራተኞች ቀን ዝግጅት በ ጥር 16 እና 17/2018 ዓ.ም በተለያዩ አበረታችና አዝናኝ መርሐ ግብሮች በደማቅ መንፈስ ተከናውኗል።

በመክፈቻው ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ተገኝተው፣ ለላቀ አፈጻጸም ያሳዩ ሰራተኞች እንዲሁም በፖስታ ገበያ (Posta Gebeya) እና ቨርቹዋል ፖስታ ሳጥን አገልግሎቶች ዝግጅት እና ትግበራ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አመራሮችና ሰራተኞች የምስጋና እውቅና እና ምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው በንግግራቸው በቀጣይ ተቋማዊ ግቦችን ለማሳካት ሁሉም ሰራተኛ በከፍተኛ መነሳሳትና ቁርጠኝነት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል። በዝግጅቱ ላይ ከሁሉም ዲስትሪክቶች በተወጣጡ ሰራተኞች መካከል የአንድነትና የቡድን መንፈስን የታየባቸው የእግር ኳስ ግጥሚያዎች ተካሂደዋል፡፡

በቀጣዩ ቀን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው በከፍተኛ አመራሮች እና በዲስትሪክት ዳይሬክተሮች መካከል የተካሄደው እና በአዝናኝነት የተሞላው የእግር ኳስ ግጥሚያ በመጨረሻ በከፍተኛ አመራሮች አሸናፊነት ተጠናቋል።

ከዚህ በተጨማሪ በሁለቱም ጾታ የዕለቱን ድባብ ከፍ ያደረጉ እና እድምተኞችን ያዝናኑ የእግር ኳስ ግጥሚያ፣ የገመድ ጉተታ፣ የማዳበሪያ ዝላይ እና እንቁላል በአፍ ይዞ መሮጥ ውድድሮች ተካሂደዋል:: በመዝጊያው እለት ለዘመናት ተቋሙን በታማኝነት ያገለገሉ እና በጡረታ ለሚለዩ አንጋፋ ሰራተኞችም የክብር አሸኛኘት ተደርጓል።

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »