ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ ወደ ኢኒስቲቲዩቱ ሲደርሱ የኢንስቲትዩቱ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ዘውዴ ለሥራ ኃላፊዎቹ የተቋሙን የስራ እቅድ እንዲሁም በተቋሙ ውስጥ ስለሚገኙ አዳዲስና ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አገልግሎቶች በተመለከተ ገለፃ አድርገውላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በተያያዘም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተቋሙ ሀገርን የሚያኮራ እና የሚያስመሰግን ሥራ እየሠራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ ለኢትዮጵያ ፖስታ ይጠቅማሉ የተባሉ የቴክኖሎጂ መገልገያዎች ለከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ የቀረቡ ሲሆን ለኢትዮጵያ ፖስታ የወደፊት ስትራቴጂ እቅድ ደጋፊ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡
ጉብኝቱ በቀጣይ ሁለቱ ተቋማት በጋራ መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መሰረት የሚጥል እንደሆነም በጉብኝቱ ላይ ተገልጿል፡፡














