የኢትዮጵያ ፖስታ እና አሐዱ ባንክ በጋራ በመሆን የተፈራረሙት የትብብር ስምምነት በመላው ኢትዮጵያ ከ1000 በላይ ቅርንጫፎች ባሉት የኢትዮጵያ ፖስታ በኩል የአሀዱ ባንክ አገልግሎቶችን በወኪልነት ለመስጠት ያለመ ነው።
የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
በተያያዘም በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ይህ ስምምነት የአሐዱ ባንክ ደንበኞች የባንክ እና ከባንክ ጋር ተያያዥ የሆኑ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በቀላሉ፣ በቅርበት እና በቀልጣፋ ሁኔታ እንዲያገኙ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።















