ዛሬ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተመሰረተበትን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አክብሯል። የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ ለመዘከር ያሳተማቸውን አራት አይነት ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።
የመከላከያ ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ በመገኘት የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ የአገራችንን ታሪክና አኩሪ ገጽታ ለቀጣዩ ትውልድም ሆነ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ የቆየ ልምድ አለው። እነዚህ ቴምብሮች የአየር ኃይሉን የ90 ዓመት የጥንካሬና የኩራት ጉዞ የሚዘክሩ ናቸው።
ታሪክን በቴምብር ሰንደን ለትውልድ እናስተላልፋለን!
መልካም 90ኛ ዓመት ለጀግናው አየር ኃይላችን!





