የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።
ይህ የትብብር ስምምነት ደንበኞች በሀገር አቀፍ ያሉትን የኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፎች በመጠቀም የM-PESA አገልግሎቶችን በቀላሉ እና በቅርበት እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል።
በተያያዘም በስምምነቱ መሰረት በኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፎች በኩል ደንበኞች፦
- ገንዘብ መላክ እና መቀበል
- የM-PESA መለያ መክፈት
- ገንዘብ ማስገባት እና ማውጣት እንዲሁም
- ሌሎች የM-PESA ዲጂታል አገልግሎቶችን በቀላሉ እና በአስተማማኝ ሁኔታ ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
በመጨረሻም ይህ ትብብር የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለህዝብ ቀላል ለማድረስ እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ለማስፋፋት የኢትዮጵያ ፖስታ እየሰራ ያለውን ስራ እንደሚያጠናክር ተነስቷል።












