የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

የተመዘገቡ ድሎች፡-

🥇 የ2025 የEMS አጠቃላይ አገልግሎት ጥራት ሽልማት (EMS Performance Award):- በአህጉራችን 1ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ 6ኛ የተቀመጠ ብቃት ማረጋገጫ!

🥈የ2025 የEMS የደንበኞች አገልግሎት ሽልማት (EMS Customer Care Award):- በአህጉራችን 1ኛ ደረጃ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በ3ኛ ነት የተቀመጠ ስኬት!

ይህም ለደንበኞቻችን የምንሰጠው አገልግሎት የዓለም አቀፍ መለኪያ መስፈርቶችን በሚገባ ሟሟላቱን፣ ለሰው ተኮር አገልግሎት የሰጠነውን ትኩረት የመሰከረ እና ከዓመት ዓመት በከፍተኛ መሻሻል ለተከታታይ ሶስት ዓመታት የተጎናጸፍነው ሽልማት ነው።

እነዚህ ዓለም አቀፍ እውቅናዎች የኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ሪፎርም ውጤታማነት ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ በዓለም አቀፍ የፈጣን መልእክት እና የሎጂስቲክስ መድረክ ላይ የሀገራችንን ተወዳዳሪነት የሚያረጋግጥ ነው።

ለሁላችሁም የኢትዮጵያ ፖስታ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ! ከጎናችን ስለሆናችሁ ከልብ እናመሠግናለን።

ይህ ድል ለቀጣይ የተሻለ አገልግሎት የገባነውን ቃል ኪዳን ማደሻችን ነው!

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »