የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽመልስ ገድለ ጊዮርጊስ የፈረሙት ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የኢትዮጰያ ፖስታን ሰፊ ተደራሽነት በመጠቀም ህብረተሰቡ የዲጂታል የህይወት መድን አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል ነው።

ወ/ሮ ትዕግስት የህይወት መድን ለዜጎች ያለውን ዘላቂ ዋስትና ጠቅሰው ተቋሙ የኢትዮጵያ ፖስታን ተደራሽነት ለመጠቀም መወሰኑ የሚደነቅ መሆኑን ሲገልጹ፣ አቶ ሽመልስ በበኩላቸው ከአንጋፋው ተቋም ጋር መስራት ለኢንሹራንስ ዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሰረት እንደሚጥል አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ ከባንኮችና ከቴሌኮም ኩባንያዎች ጋር በዲጂታል ፋይናንስ ሲሰራ የቆየ ቢሆንም፣ የዲጂታል የህይወት መድን አገልግሎት መስጠት የሚጀምርበት ይህ ስምምነት ለመጀመሪያ ጊዜ የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »