የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሀገሪቱን የግብይት እና የሎጀስቲክስ ሰንሰለት በማቀናጀት ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።

የፊርማ ሥነ-ሥርዓቱን የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ በኃይሉ ንጉሴ ተፈራርመዋል።

ይህ ስምምነት የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽንን ዘርፈ ብዙ የእህል፣ የጥራጥሬ እና የአትክልት ምርቶች ለህብረተሰቡ በስፋት ለማድረስ የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የኢትዮጵያ ፖስታ ያለውን ግዙፍ የሎጀስቲክስ አቅም፣ የትራንስፖርት መዋቅር እና በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ቅርንጫፎቹን ተደራሽነት በመጠቀም ምርቶቹ በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ዜጎች እንዲቀርቡ እንደሚደረግ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ በኃይሉ ንጉሴ በበኩላቸው ይህ ስምምነት ምርቶችን በቀጥታ ከምንጩ (ከገበሬው) ወደ ሸማቹ በማድረስ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጡም በላይ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን የጎላ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል።

በተጨማሪም ከሀገራዊ ፋይዳ አንጻር ይህ ጥምረት መንግስት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየሠራቸው ለሚገኙ ሥራዎች በከፍተኛ ደረጃ የሚያግዝ ነው።

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »