የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።
የተመዘገቡ ድሎች፡-
🥇 የ2025 የEMS አጠቃላይ አገልግሎት ጥራት ሽልማት (EMS Performance Award):- በአህጉራችን 1ኛ በዓለም አቀፍ ደረጃ 6ኛ የተቀመጠ ብቃት ማረጋገጫ!
🥈የ2025 የEMS የደንበኞች አገልግሎት ሽልማት (EMS Customer Care Award):- በአህጉራችን 1ኛ ደረጃ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በ3ኛ ነት የተቀመጠ ስኬት!
ይህም ለደንበኞቻችን የምንሰጠው አገልግሎት የዓለም አቀፍ መለኪያ መስፈርቶችን በሚገባ ሟሟላቱን፣ ለሰው ተኮር አገልግሎት የሰጠነውን ትኩረት የመሰከረ እና ከዓመት ዓመት በከፍተኛ መሻሻል ለተከታታይ ሶስት ዓመታት የተጎናጸፍነው ሽልማት ነው።
እነዚህ ዓለም አቀፍ እውቅናዎች የኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ሪፎርም ውጤታማነት ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ በዓለም አቀፍ የፈጣን መልእክት እና የሎጂስቲክስ መድረክ ላይ የሀገራችንን ተወዳዳሪነት የሚያረጋግጥ ነው።
ለሁላችሁም የኢትዮጵያ ፖስታ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ! ከጎናችን ስለሆናችሁ ከልብ እናመሠግናለን።
ይህ ድል ለቀጣይ የተሻለ አገልግሎት የገባነውን ቃል ኪዳን ማደሻችን ነው!









