Ethiopost Receives the 2023 Postal Excellence Award

Ethiopost receives the 2023 Postal Excellence Award in Riyadh as the lead for the Africa Region! Our Deputy CEO, Gashaw Mersha, had the honor of receiving the award on our behalf.

This recognition is the result of Ethiopost’s exemplary performance across key metrics evaluating designated postal operators. These past few years, Ethiopost has been hard at work implementing institutional reforms that address service quality, delivery, speed, and accessibility, among many others. We are proud that this effort has culminated in this recognition as a regional leader in postal excellence by the Universal Postal Union’s Extraordinary Congress held in Riyadh, Saudi Arabia.


የኢትዮጵያፖስታ በሪያድ የአፍሪካ ሪጅን የPostal Excellence Award ተሸላሚ ሆነ!

የዓለም ፖስታ ሕብረት በየዓመቱ በሚያደርገው የፖስታ አገልግሎት ሰጪዎች ምዘና የኢትዮጵያ ፖስታ በ2023 ዓ.ም. የአፍሪካ ሪጅን አሽናፊ መሆኑ ተገለጸ። ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጋሻው መርሻ ሽልማቱን ተቀብለዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ባለፉት ዓመታት ተቋማዊ ሪፎርሞችን በመተግበር የአገልግሎት አሠጣጥ ማሻሻያዎች፣ የመልዕክት ፍጥነትና ተደራሽነት ላይ በርካታ ለውጦች እንዳመጣ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የዓለም ፖስታ ሕብረት በሚያደርገው የአግልግሎት ጥራት ምዘና ከዓመት ዓመት አፈጻጸሙን ሲያሻሽል ቆይቶ ዛሬ በሪያድ፣ ሳውዲ አረቢያ በተደረገው የሕብረቱ ልዩ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ ሪጅንን በመምራት የፖስታ ልሕቀት ሽልማት ተቀብሏል።

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »