የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መሥሪያ ቤት ለ3ኛ ጊዜ በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

በክበረ በዓሉ ላይ “የፖስታ አገልግሎት ከቀላል የመልዕክት መለዋወጫነት ባሻገር የሀገርን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ትረካዎች የሰነደ ታሪካዊ አምባሳደር መሆኑ የተነሳ ሲሆን” በዚህ ፈታኝና በተከፋፈለ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ ውስጥ ሙዚየሞች የሀገሪቱን ዘመናዊነት፣ የቆየ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የጋራ እሴቶችን በማጉላት ሕዝቦችን የማገናኘት ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ተገልጿል፡፡

በመቀጠልም በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም በሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ደረጃዎች ተገምግሞ የሰርተፊኬት ሽልማት የተበረከተለት ሲሆን የእውቅናውን ሰርተፊኬት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ ለኢትዮጵያ ፖስታአስረክበዋል፡፡

በዚህም ተቋሙ የሀገርን ቅርስ በአግባቡ ጠብቆ ለማቆየትና ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ እያደረገ ላለው ቁርጠኝነት የተሰጠ ትልቅ ማረጋገጫ ነው ተብሏል።

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »