የኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ዲጂታል የገበያ ማዕከልን ለማቅረብ ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ከሲኤስኤም አፍሪኮም ጋር በጋራ ተፈራርሟል።

በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሃገር ውስጥ እና አለም አቀፍ ዲጂታል የገበያ እድል ለመፍጠር የተዘጋጀው ፕሮጀክት፥ በዛሬው እለት ለየኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ዲጂታል የገበያ ማእከልን ለማቅረብ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ሲ.ኤስ.ኤም ከአፍሪኮም ጋር በጋራ በመሆን በዛሬው እለት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ ይህን የኢ-ኮሜርስ ዲጂታል የገበያ ማእከልን በመምራት ብሎም የሎጂስቲክስ ክፍተቱን በመሙላት እንከን የለሽ እና ቀልጣፋ የአገልግሎት አቅርቦትን ለማረጋግጥ የሚሰራ ይሆናል።

ይህ ፕሮጀክት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በመደገፍ የኢ-ኮሜርስ መልክዓ ምድሩን ለመለወጥ በማለም የላቀ እርምጃ ወደፊት ያራምዳል። ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ጠንካራ የገበያ ቦታ በመፍጠር ለዳበረ ዲጂታል ኢኮኖሚ መንገድም ይከፍታል።

Follow us on our social media platforms | Facebook | Telegram | LinkedIn | Twitter | Instagram | Pinterest | TikTok |

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »