የኢትዮዽያ ፖስታ በስኬት ጉዞ ላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጹ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ ለውጡን ተከትሎ በተሰሩ ተከታታይ የሪፎርም ሥራዎች የኢትዮጵያ ፖስታ ከነበሩበት ችግሮች ተላቆ በብዙ የስራ ትጋትና ጥረት በአንዳንድ አገልግሎቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር የሚያችል አቅም እንደገነባ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ አክለውም እዚህ ስኬት ላይ የተደረሰው በዋነኝነት የደንበኞች ፍላጎትና የፖስታ አገልግሎት ላይ ጥልቅ ጥናቶችን በማድረግ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ የሀገር ውሰጥ እና ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በማስፋፋት ፣በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት እንዲሁም የአገልግሎት መስጫዎችን ምቹ የማድረግ ሥራዎችን በመስራት እንደሆነ ተናግረዋል።

በተጨማሪም አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የኢትዮጵያ ፖስታ በዚህ ሁለንተናዊ ለውጥ በመንግስትም ሆነ በአለም አቀፉ ፖስታ ህብረት ተሸላሚ መሆን እንደቻለ፤ ጥረቶቹንም አጠናክሮ በመቀጠል እና ቀሪ ክፍተቶችን በመሙላት ለተሻለ ስኬት እየተንደረደረ ያለ ልማታዊ የመንግስት ተቋም እንደሆነም ገልፀዋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »