የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ውሎች ዝግጅት በኢትዮጵያ ፖስታ

የኢትዮጵያ ፖስታ ከሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት በተሰጠው ውክልና መሰረት የውል ጽሁፎችን በማሰናዳት እናንተን ለማገልገል ከዛሬ ሐምሌ 1 ፣ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተመረጡ ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት ጀምራል።

የምንሰጠው አገልግሎት በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት የሚቀርቡ
✅ የውክልና ስልጣን ምዝገባ
✅ የብድር ውል ምዝገባ
✅ የንብረት ሽያጭ ውል ምዝገባ
✅ የሊዝ ውል ምዝገባ
✅ የንብረት ልገሳ ውል ምዝገባ
✅ የውጭ ሰነዶች ምዝገባ እንዲሁም በ ውጪ ጉዳይ የተረጋገጡ የውጭ ሰነዶች ምዝገባ ውሎች


በዛሬው እለት የተጀመረውን አገልግሎታችንን በዋናው ፖስታ ቤት፣ በልደታ ቅርንጫፍ፣ ቦሌ መድኃኒአለም ቅርንጫፍ፣ አራት ኪሎ ቅርንጫፍ እና በቤተል ቅርንጫፎቻችን ማግኘት እንደምትችሉ እንገልጻለን፡፡

በልህቀት ልናገለግልዎ ዝግጁ ነን!!

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »