የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

በዚሁ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮመርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በቀለ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍን ዲጂታላይዝና ዘመናዊ ከማድረግ አኴያ ኢትዮጵያ ፖስታ እየተጫወተ ስላለው ጉልህ ሚና አስረድተዋል። በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ በአለም አቀፍ የንግድ ማእከል እና #ICTET የተዘጋጀው ወርክሾፕ ፣ የ #AfCFTA (የአፍሪካ ኮንቲኔንታል ነፃ የንግድ ቀጠና) ትግበራን ለመደገፍ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎችን ፣የሎጂስቲክስ ሞዴሎችን እና አዳዲስ የመፍትሄ ማሳያ መንገዶች ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ብሎም በመላው ዓለም የሚከናወኑ የንግድና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ቀልጣፋ፣ አካታች እና ዘላቂ የሚያደርጉ የሎጂስቲክስ መፍትሄዎችን ለማምጣት የኢትዮጵያ ፖስታ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በወርክሾፑ ላይ ተገልጿል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የአየር ኃይላችንን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጃቸውን አራት አይነት ታሪካዊ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።

ዛሬ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተመሰረተበትን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አክብሯል። የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ ለመዘከር ያሳተማቸውን አራት አይነት ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በይፋ አስመረቀ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ያበለጸጋቸውን የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመርቋል፡፡

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »