የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

በዚሁ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮመርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በቀለ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍን ዲጂታላይዝና ዘመናዊ ከማድረግ አኴያ ኢትዮጵያ ፖስታ እየተጫወተ ስላለው ጉልህ ሚና አስረድተዋል። በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ በአለም አቀፍ የንግድ ማእከል እና #ICTET የተዘጋጀው ወርክሾፕ ፣ የ #AfCFTA (የአፍሪካ ኮንቲኔንታል ነፃ የንግድ ቀጠና) ትግበራን ለመደገፍ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎችን ፣የሎጂስቲክስ ሞዴሎችን እና አዳዲስ የመፍትሄ ማሳያ መንገዶች ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ብሎም በመላው ዓለም የሚከናወኑ የንግድና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ቀልጣፋ፣ አካታች እና ዘላቂ የሚያደርጉ የሎጂስቲክስ መፍትሄዎችን ለማምጣት የኢትዮጵያ ፖስታ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በወርክሾፑ ላይ ተገልጿል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »