የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

በዚሁ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮመርሻል ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በቀለ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍን ዲጂታላይዝና ዘመናዊ ከማድረግ አኴያ ኢትዮጵያ ፖስታ እየተጫወተ ስላለው ጉልህ ሚና አስረድተዋል። በትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ በአለም አቀፍ የንግድ ማእከል እና #ICTET የተዘጋጀው ወርክሾፕ ፣ የ #AfCFTA (የአፍሪካ ኮንቲኔንታል ነፃ የንግድ ቀጠና) ትግበራን ለመደገፍ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂዎችን ፣የሎጂስቲክስ ሞዴሎችን እና አዳዲስ የመፍትሄ ማሳያ መንገዶች ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነበር።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ብሎም በመላው ዓለም የሚከናወኑ የንግድና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ቀልጣፋ፣ አካታች እና ዘላቂ የሚያደርጉ የሎጂስቲክስ መፍትሄዎችን ለማምጣት የኢትዮጵያ ፖስታ እያደረገ ያለውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በወርክሾፑ ላይ ተገልጿል።

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »